News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከግሎባል ኤሲአይ (Global ACI) ጋር ያለውን የባለብዙ ወገን የጋራ እውቅና ስምምነት በፊርማ አደሰየኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የአለምአቀፍ ዕውቅና ትብብር (GLOBAL ACCREDITATION COOPERATION INCORPORATED) ሙሉ አባል ሆነ::በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ግዜ ከነሐሴ 24-29/2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው ‘የኢትዮጵያ ይግዙ ‘ የንግድ ሳምንት ላይ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ለጎብኝዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡Call for Healthcare Accreditation Surveyorየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የኢስኳ ISQua ይፋዊ ሙሉ አባል በመሆን አለም አቀፍ የጤና ዘርፍ አክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት መስጠት የሚያስችለውን እውቅና አጊንቷል።የኢትዮጵያ አክሬድቴሽን አገልግሎት 17ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ።የመ/ቤቱ ሰራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱጥራትን ማስጠበቅ የሁሉም አካላት አንገብጋቢ ጉዳይ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠ

የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ለተስማሚነት ምዘና ተቋማት የሚሰጠውን የአክሪዲቴሽን  አገልግሎት የበለጠ ተደራሽ ለማድርግ በካሊብሬሽን ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኝ ማድርግ እንደሚገባ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ተናገሩ

ዋና ዳይሬክተሩ አቶ አርአያ ፍስሃ ዛሬ ለፍተሻ ላቦራቶሪ አሰሰሮች ዓመታዊ  ኮንፍረንስ ሲጀመር እንደተናገሩት በፍተሻ ላቦራቶሪ መስክ የአክሪዲቴሸን አገልግሎትን ለማስፋት ቅድሚያ የካሊብሬሸን ላቦራቶሪዎች ወደ አክሪዲቴሸን ሊመጡ ይገባል

የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ለካሊብሬሸን ላቦራቶሪዎች ዓለም አቀፍ እውቅና ለመስጠት ዝግጅት ቢያደረግም አመልካች ባለመኖሩ አገልግሎቱን መስጠት አለመቻሉንና አገልግሎቱን ካልሰጠ ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግምገማ እንዲደረግበት መጠየቅ ስለማይችል ከሌሎች የተስማሚነት ምዘና ዘርፎች ካሊብሬሸን ወደኃላ ቀርቷል ብለዋል

በሰርቲፍኬሸን ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት ተቋሙ ዓlም አቀፍ ግምገማ እንደተካሔደበት አስታውሰው በሰርቲፍኬሸን  በግምገማ ወቅት የተገኙትን አነስተኛ ክፍተቶች ተቋሙ ማስተካከሉንና በቅርቡም ዓለም አቀፍ እውቅናው እንደሚገኝ ጠቁመዋል

የአሰሰሮች ዓመታዊ ኮንፍረንስ ዋና ዓላማ በዓመት ውስጥ የአሰስመንት ስራዎች ሲሰሩ በስራ ላይ ያጋጠሙ ክፍተቶችን በመገምገም በቀጣይ ክፍተቶቹን ለማስተካከል፣ በአሰሰሮች መካከል በአንድ ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አረዳድ እንዲይዙ ማድረግና አዳዲስ የተለወጡ ሰነዶች ካሉ በነሱ ላይ ግንዛቤ ለመስጠት መሆኑንም ጠቁመዋል

የአክሪዲቴሽን አገልግሎትን ለማስፋት የካሊብሬሽን ዘርፍን ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኝ ማድርግ ያስፈልጋል ተባለ