News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

=============================

አዲስ አበባ 10/11/ 2015

ኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን በላይ ችግኝ የመትከል መርሐ ግብሯን ማሳካቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡

የተዛባ አየር፣ የተራቆተ ምድር ለትውልድ አናወርስም ብላችሁ፤ ጎሕ ሳይቀድ ወደ ተራሮችና ሸለቆዎች፣ ወደ ሜዳዎችና ሸንተረሮች ተሠማርታችሁ 566 ሚልዮን ዛፎች መተከላቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

በዚህም መሰረት አገራዊ ጥሪውን መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በመገኘት የአረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር የታሪኩ ተጋሪ መሆን ችለዋል፡፡

በችግኝ ተከላው ላይ አገልግሎቱን ለረጅም ዓመታት ሲያገለግሉ ቆይተው ሐምሌ 05 ቀን 2015ዓ.ም ጀምሮ በቅርቡ ስራቸውን የለቀቁት የአገልግሎቱ የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት ተሰማ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡ