News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከግሎባል ኤሲአይ (Global ACI) ጋር ያለውን የባለብዙ ወገን የጋራ እውቅና ስምምነት በፊርማ አደሰየኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የአለምአቀፍ ዕውቅና ትብብር (GLOBAL ACCREDITATION COOPERATION INCORPORATED) ሙሉ አባል ሆነ::በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ግዜ ከነሐሴ 24-29/2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው ‘የኢትዮጵያ ይግዙ ‘ የንግድ ሳምንት ላይ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ለጎብኝዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡Call for Healthcare Accreditation Surveyorየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የኢስኳ ISQua ይፋዊ ሙሉ አባል በመሆን አለም አቀፍ የጤና ዘርፍ አክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት መስጠት የሚያስችለውን እውቅና አጊንቷል።የኢትዮጵያ አክሬድቴሽን አገልግሎት 17ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ።የመ/ቤቱ ሰራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱጥራትን ማስጠበቅ የሁሉም አካላት አንገብጋቢ ጉዳይ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠ

=============================

አዲስ አበባ 10/11/ 2015

ኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን በላይ ችግኝ የመትከል መርሐ ግብሯን ማሳካቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡

የተዛባ አየር፣ የተራቆተ ምድር ለትውልድ አናወርስም ብላችሁ፤ ጎሕ ሳይቀድ ወደ ተራሮችና ሸለቆዎች፣ ወደ ሜዳዎችና ሸንተረሮች ተሠማርታችሁ 566 ሚልዮን ዛፎች መተከላቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

በዚህም መሰረት አገራዊ ጥሪውን መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በመገኘት የአረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር የታሪኩ ተጋሪ መሆን ችለዋል፡፡

በችግኝ ተከላው ላይ አገልግሎቱን ለረጅም ዓመታት ሲያገለግሉ ቆይተው ሐምሌ 05 ቀን 2015ዓ.ም ጀምሮ በቅርቡ ስራቸውን የለቀቁት የአገልግሎቱ የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት ተሰማ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡ