News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

ነሀሴ 29 ቀን 2015ዓ.ም

አዲስ አበባ

አቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ ሹመታቸውን ተከትሎ በአገልግሎቱ ዋና ዳይሬተር ቢሮ በመገኘት ከአገልግሎቱ የሥራ አመራር ኮሚቴ አባላት ጋር ትውውቅ እና የሥራ ርክክብ አድርገዋል፡፡

አገልግሎቱ ያለበትን ደረጃ እና በ2015 በጀት ዓመት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን እንዱሁም በቀጣ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ የአገልግሎቱ የዋና ዳይሬከተር ተወካይ በመሆኑ ላለፉት ሁለት ወራት ያገለገሉት የአገልግሎቱ የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ውብታየሁ ባቲ ሰፊ ያለ ማብራሪያ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል፡፡

በዚህም መሰረት ከዓለም አቀፍ አቻ ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙት በማጠናከር ዓለም አቀፍ ዕውቅና የማስቀጠል ስራዎች፣የ2016 በጀት ዓመት የዕቅድ ዝግጅት፣የአገልግሎቱ የሰው ሃይል አደረጃጀት፣አዲስ በመገንባት ላይ ያለው የአገልገሎቱ ሕንጻ ያለበትን ደረጃ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች በማብራሪያው  ተዳሰዋል፡፡

ማብራሪያውን ተከትሎ በቀጣይ መሰራት ያለባቸው ስራዎች እና የትኩረት አቅጣጫዎችን መሰረት በማድረግ ሁሉም የስራ አመራር አባላት ስራዎቻቸውን በኃላፊነት ስሜት እንዲወጡ ያሳሰቡት ዋና ዳይሬከተሩ እንደ መሪ ከእሳቸው የሚጠበቁ ድጋፎችን እንደሚያደርጉ እንዱሁም የሚጠበቅባቸውን የአመራር ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ዋና ዳይሬክተሩ ከአገልግሎቱ አመራር አባላት እንዲሁም  ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር  እና ከተጠሪ ተቋማቱ አመራሮች ጋር በመሆን “የውሃ ሀብታችን ለብልፅግናችን” በሚል መሪ ቃል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የውሃና ኢነርጂ አውደ ርዕይ ጎብኝተዋል።

በአውደ ርዕዩ ላይ የውሃ ሃብታችን ጥራቱን የጠበቀና ለሚፈለገው አገልግሎት፣ ለመስኖ፣ ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ ለኢንዱስትሪ፣ ለመዝናኛ እንዲሁም ለግድብና ለተለያዩ አገልግሎቶች እንዲውል ለማስቻል ሚ/ር መስሪያ ቤቱ የተለያዩ ዘመናዊ የውሃ ጥራት ማስጠበቂያ መሳሪያዎችን ጥቅም ላይ እያዋለ መሆኑንም  መመልከት ተችሏል፡፡  

አቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ