News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከግሎባል ኤሲአይ (Global ACI) ጋር ያለውን የባለብዙ ወገን የጋራ እውቅና ስምምነት በፊርማ አደሰየኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የአለምአቀፍ ዕውቅና ትብብር (GLOBAL ACCREDITATION COOPERATION INCORPORATED) ሙሉ አባል ሆነ::በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ግዜ ከነሐሴ 24-29/2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው ‘የኢትዮጵያ ይግዙ ‘ የንግድ ሳምንት ላይ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ለጎብኝዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡Call for Healthcare Accreditation Surveyorየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የኢስኳ ISQua ይፋዊ ሙሉ አባል በመሆን አለም አቀፍ የጤና ዘርፍ አክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት መስጠት የሚያስችለውን እውቅና አጊንቷል።የኢትዮጵያ አክሬድቴሽን አገልግሎት 17ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ።የመ/ቤቱ ሰራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱጥራትን ማስጠበቅ የሁሉም አካላት አንገብጋቢ ጉዳይ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠ

መጋቢት 01 ቀን 2015ዓ.ም

‘’ዓለማችን ያለሴቶች ዋጋም ውበትም የላትም’’

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓልን በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት መሰብሰቢያ አዳራሽ አከበሩ።

ዓለም ያለሴቶች ዋጋም ውበትም የላትም ሲሉ በዓሉ ላይ በመገኘት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት ተሰማ ሴቶችን ማብቃት የስልጣኔ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።ሴቶችን ማብቃት ቤተሰብን፣ጎረቤትን እንዲሁም በአጠቃላይ ህብረተሰብን ማብቃት መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ መሰረት አገራችን አሁን ካለችበት የከፋ ድህነት ማላቀቅ የሚቻለው የሴቶችን ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ አቅም ማሳደግ ስንችል መሆኑን ተናግረዋል።

አብዛኞቹ የኢትዮጵያ እናቶች በትልቅ መስዋዕትነት ለዚህ ያበቁን መሆኑን ጠቅሰው ለሴቶች ያላቸው ክብር ከፍተኛ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ ህህህከሴቶች ጎን በመቆም የሰለጠነ ማህበረሰብ መፍጠር እንዳለብን በማሳሰብ መልካም የሴቶች ቀን በዓል እንዲሆን ለተሳታፊዎች ተመኝተዋል።

በበዓሉ ላይ የተገኙት የአንዴ ማማ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ መቅደስ ተሾመ የድርጅቱ ፕሮጀክት የሆነው “የእናት መንፈስ ፍቅር ፕሮጀክት” ዓላማ ሴት የህብረተሰብ ክፍሎችን የማብቃትና የአካባቢን የብክለት የመጠበቅ ስራዎች ላይ ገለጻ አቅርበዋል።የወደቁ ወረቀቶችን በመሰብሰብ እና መልሶ ስራ ላይ በማዋል በርካታ እናቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ በገለጻው አብራርተዋል።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና  ዳይሬክተር መሰረት በቀለ(ዶ/ር) ለአንዴ ማማ ድርጅት ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ ለድርጅቱ ድጋፍ ለማድረግ በኢንስቲትዩቱ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተመሳሳይ ድርጅቱ ለሚያከናውናቸው ስራዎች ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ አገልግሎቱ የወደቁ ወረቀቶችን በመሰብሰብ ለድርጅቱ ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪ ድርጅቱ የሚያመርታቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ድጋፍ እንደሚያደርጉ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት ተሰማተ ናግረዋል።

ከሴቶች መብት ጋር ተይይዞ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 35 ላይ የተደነገጉ መብቶች ላይ በአገልግሎቱ የህ ግባለሙያ በአቶ መሀመድ አረቡ ገለጻ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።በመጨረሻም ለአገራችን ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ሴቶች እና የሰሩዋቸው ገድሎች ላይ በአገልግሎቱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቡድን መሪ በወ/ሮ አዜብ ሰለሞን ገለጻ ቀርቦ ውይይት በማድረግ በዓሉ ተጠናቋል።

በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ112ኛ እንዲሁም በአገራችን ለ47 ጊዜ’’ እኔ የእህቴ ጠባቂነኝ’’ በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።

የአገልግሎቱ የስራ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች የዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን በዓልን አከበሩ