News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

መጋቢት 01 ቀን 2015ዓ.ም

‘’ዓለማችን ያለሴቶች ዋጋም ውበትም የላትም’’

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓልን በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት መሰብሰቢያ አዳራሽ አከበሩ።

ዓለም ያለሴቶች ዋጋም ውበትም የላትም ሲሉ በዓሉ ላይ በመገኘት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት ተሰማ ሴቶችን ማብቃት የስልጣኔ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።ሴቶችን ማብቃት ቤተሰብን፣ጎረቤትን እንዲሁም በአጠቃላይ ህብረተሰብን ማብቃት መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ መሰረት አገራችን አሁን ካለችበት የከፋ ድህነት ማላቀቅ የሚቻለው የሴቶችን ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ አቅም ማሳደግ ስንችል መሆኑን ተናግረዋል።

አብዛኞቹ የኢትዮጵያ እናቶች በትልቅ መስዋዕትነት ለዚህ ያበቁን መሆኑን ጠቅሰው ለሴቶች ያላቸው ክብር ከፍተኛ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ ህህህከሴቶች ጎን በመቆም የሰለጠነ ማህበረሰብ መፍጠር እንዳለብን በማሳሰብ መልካም የሴቶች ቀን በዓል እንዲሆን ለተሳታፊዎች ተመኝተዋል።

በበዓሉ ላይ የተገኙት የአንዴ ማማ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ መቅደስ ተሾመ የድርጅቱ ፕሮጀክት የሆነው “የእናት መንፈስ ፍቅር ፕሮጀክት” ዓላማ ሴት የህብረተሰብ ክፍሎችን የማብቃትና የአካባቢን የብክለት የመጠበቅ ስራዎች ላይ ገለጻ አቅርበዋል።የወደቁ ወረቀቶችን በመሰብሰብ እና መልሶ ስራ ላይ በማዋል በርካታ እናቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ በገለጻው አብራርተዋል።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና  ዳይሬክተር መሰረት በቀለ(ዶ/ር) ለአንዴ ማማ ድርጅት ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ ለድርጅቱ ድጋፍ ለማድረግ በኢንስቲትዩቱ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተመሳሳይ ድርጅቱ ለሚያከናውናቸው ስራዎች ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ አገልግሎቱ የወደቁ ወረቀቶችን በመሰብሰብ ለድርጅቱ ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪ ድርጅቱ የሚያመርታቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ድጋፍ እንደሚያደርጉ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት ተሰማተ ናግረዋል።

ከሴቶች መብት ጋር ተይይዞ በኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 35 ላይ የተደነገጉ መብቶች ላይ በአገልግሎቱ የህ ግባለሙያ በአቶ መሀመድ አረቡ ገለጻ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።በመጨረሻም ለአገራችን ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ሴቶች እና የሰሩዋቸው ገድሎች ላይ በአገልግሎቱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቡድን መሪ በወ/ሮ አዜብ ሰለሞን ገለጻ ቀርቦ ውይይት በማድረግ በዓሉ ተጠናቋል።

በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ112ኛ እንዲሁም በአገራችን ለ47 ጊዜ’’ እኔ የእህቴ ጠባቂነኝ’’ በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።

የአገልግሎቱ የስራ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች የዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን በዓልን አከበሩ