News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሪዲቴሸን ጽ/ቤት በኮንስትራክሽንንና በብረታብረት ዘርፍ ለተሰማሩ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪዎች የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጠ፡፡

ጽ/ቤቱ ባዘጋጀው ለኮንስትራክሽንንና በብረታብረት የማምረቻ ተቋማትና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች  የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መክፈቻ ላይ የጽ/ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ጽጌመላክ ባደረጉት ንግግር ተቋማት ለህብረተሰቡ የሚያቀርቡት ምርት ጥራን የጠበቀ እንዲሆን አንዱ መንገድ የአክሪዲቴሸን ተጠቃሚ መሆን ነው፡፡

እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ የኮንስትራክሽን ዘርፉ በሃገሪቱ በፍጥነት እያደገ ያለ ዘርፍ በመሆኑ የኮንስትራክሽን ግብአት የሚያቀርቡ ተቋማት ለምርት ፍተሻ የሚጠቀሙባቸው ላቦራቶሪዎቻቸው ወደ አክሪዲቴሽን ቢመጡ የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

ጽ/ቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በዝርዝር ያቀረቡት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የግንዛቤ ስልጠናው በዋናነት ተቋማት ጽ/ቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች አውቀው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡

የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን የሰጡት የጽ/ቤቱ የኢንስፔክሽን አክሪዲቴሸን ባለሙያ አቶ ዘውዱ ገብረሚካኤል ተቋማት ምርቶቻቸው ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት ጥራቱን የጠበቀ ለማድርግ አንዱ መንገድ አክሪዲት የሆኑ የኢንስፔክሽን ተቋማትን መጠቀም አልያም ላቦራቶሪዎቻቸውን  አክሪዲት ማስደረግ የኢንስፔክሽን ስርአታቸውን ማጠናከር፣ አክሪዲት በሆኑ ላቦራቶሪዎች መጠቀም ነው ብለዋል፡፡

አክሪዲቴሸን የአጭር ጊዜ ሥራ እንዳልሆነ የተናገሩት አቶ ዘውዱ ተቋማት የአክሪዲቴሸን ተጠቃሚ ለመሆን ጠንክረው ሊሰሩ ይገባል፡፡ አክሪዲቴሽን ለደንበኞች እምነት ይሰጣል፣ምርትና አገልግሎቶች ተወዳዳሪ እነዲሆኑ ያደርጋል ሲሉም ተናግርዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ለተለየያ ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ