News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከግሎባል ኤሲአይ (Global ACI) ጋር ያለውን የባለብዙ ወገን የጋራ እውቅና ስምምነት በፊርማ አደሰየኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የአለምአቀፍ ዕውቅና ትብብር (GLOBAL ACCREDITATION COOPERATION INCORPORATED) ሙሉ አባል ሆነ::በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ግዜ ከነሐሴ 24-29/2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው ‘የኢትዮጵያ ይግዙ ‘ የንግድ ሳምንት ላይ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ለጎብኝዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡Call for Healthcare Accreditation Surveyorየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የኢስኳ ISQua ይፋዊ ሙሉ አባል በመሆን አለም አቀፍ የጤና ዘርፍ አክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት መስጠት የሚያስችለውን እውቅና አጊንቷል።የኢትዮጵያ አክሬድቴሽን አገልግሎት 17ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ።የመ/ቤቱ ሰራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱጥራትን ማስጠበቅ የሁሉም አካላት አንገብጋቢ ጉዳይ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሪዲቴሸን ጽ/ቤት በኮንስትራክሽንንና በብረታብረት ዘርፍ ለተሰማሩ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪዎች የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጠ፡፡

ጽ/ቤቱ ባዘጋጀው ለኮንስትራክሽንንና በብረታብረት የማምረቻ ተቋማትና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች  የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መክፈቻ ላይ የጽ/ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ጽጌመላክ ባደረጉት ንግግር ተቋማት ለህብረተሰቡ የሚያቀርቡት ምርት ጥራን የጠበቀ እንዲሆን አንዱ መንገድ የአክሪዲቴሸን ተጠቃሚ መሆን ነው፡፡

እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ የኮንስትራክሽን ዘርፉ በሃገሪቱ በፍጥነት እያደገ ያለ ዘርፍ በመሆኑ የኮንስትራክሽን ግብአት የሚያቀርቡ ተቋማት ለምርት ፍተሻ የሚጠቀሙባቸው ላቦራቶሪዎቻቸው ወደ አክሪዲቴሽን ቢመጡ የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

ጽ/ቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በዝርዝር ያቀረቡት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የግንዛቤ ስልጠናው በዋናነት ተቋማት ጽ/ቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች አውቀው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡

የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን የሰጡት የጽ/ቤቱ የኢንስፔክሽን አክሪዲቴሸን ባለሙያ አቶ ዘውዱ ገብረሚካኤል ተቋማት ምርቶቻቸው ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት ጥራቱን የጠበቀ ለማድርግ አንዱ መንገድ አክሪዲት የሆኑ የኢንስፔክሽን ተቋማትን መጠቀም አልያም ላቦራቶሪዎቻቸውን  አክሪዲት ማስደረግ የኢንስፔክሽን ስርአታቸውን ማጠናከር፣ አክሪዲት በሆኑ ላቦራቶሪዎች መጠቀም ነው ብለዋል፡፡

አክሪዲቴሸን የአጭር ጊዜ ሥራ እንዳልሆነ የተናገሩት አቶ ዘውዱ ተቋማት የአክሪዲቴሸን ተጠቃሚ ለመሆን ጠንክረው ሊሰሩ ይገባል፡፡ አክሪዲቴሽን ለደንበኞች እምነት ይሰጣል፣ምርትና አገልግሎቶች ተወዳዳሪ እነዲሆኑ ያደርጋል ሲሉም ተናግርዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ለተለየያ ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ