News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከግሎባል ኤሲአይ (Global ACI) ጋር ያለውን የባለብዙ ወገን የጋራ እውቅና ስምምነት በፊርማ አደሰየኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የአለምአቀፍ ዕውቅና ትብብር (GLOBAL ACCREDITATION COOPERATION INCORPORATED) ሙሉ አባል ሆነ::በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ግዜ ከነሐሴ 24-29/2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው ‘የኢትዮጵያ ይግዙ ‘ የንግድ ሳምንት ላይ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ለጎብኝዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡Call for Healthcare Accreditation Surveyorየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የኢስኳ ISQua ይፋዊ ሙሉ አባል በመሆን አለም አቀፍ የጤና ዘርፍ አክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት መስጠት የሚያስችለውን እውቅና አጊንቷል።የኢትዮጵያ አክሬድቴሽን አገልግሎት 17ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ።የመ/ቤቱ ሰራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱጥራትን ማስጠበቅ የሁሉም አካላት አንገብጋቢ ጉዳይ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠ

ሚያዝያ 05 ቀን 2015ዓ.ም

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከሚሰጣቸው የአክሬዲቴሽን አገልግሎቶች መካካል የሕክምና ላቦራቶሪ አክሪዲቴሽን ISO 15189:2012 ን   አዲስ በተከለሰው  ISO 15189:2022 ለመተካት እስከ  ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም የሚቆይ የሽግግር ዕቅድ አዘጋጀ፡፡ በዚህም መሰረት አገልግሎቱን ለሚፈልጉ አዲስ አመልካቾች  ከመስከረም 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ በተከለሰው  ISO 15189:2022  የሚስተናገዱ መሆኑን አግልግሎቱ አስታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ቀደም ብለው አገልግሎቱን ለማግኘት እዉቅና ያገኙ እንዲሁም በሂደት ላይ ያሉ ደንበኞች ከሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በኃላ  አሰስመንት የሚከናወነው  አዲስ በተከለሰው መሰረት ISO 15189:2022 እንደሚሆን የአገልግሎቱ የጥራት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አየለ ገልጸዋል፡፡ አክለውም የሕክምና ላቦራቶሪ የተሰማሚነት ምዘና ተቋማት የተከለሰውን አዲሱን የህክምና ላቦራቶሪ ደረጃ ISO 15189:2022) የሽግግር ዕቅዱ ዝርዝር ይዘት ከአገልግሎቱ ድረ-ገጽ ላይ https://eas-eth.org/forms/ በማውረድ ማስተካከያዎችን በማድረግ ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀ