News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ማኔጅመንትና የቴክኒክ ባለሙያዎች የአገልግሎቱን ፖሊሲዎችና ዓላማዎች በአግባቡ ተረድተው አገልግሎቱን ሲሰጡ በእውቀት ላይ ተመስርተው ሊሆኑ እንደሚገባ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ገለፁ

ዋና ዳይሬክተሩ አቶ አርአያ ፍስሃ ዛሬ የካቲት 16ቀን 2014ዓ.ም በአዳማ በተጀመረው የአገልግሎቱ የማኔጅመንትና የቴክኒካል ባለሙያዎች ISO/IEC 17011:2017 በዓለም አቀፉ ደረጃ ላይ በተጀመረው ስልጠና ላይ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ለሌሎች ተቋማት ሶስተኛ ወገን በመሆን ዓለም አቀፍ ምስክርነት የሚሰጥ በመሆኑ ራሱ አስቀድሞ ዓለም አቀፉን ደረጃ በሚገባ ሊረዳ ይገባል

ብቃት በአንድ ቀን የሚገነባ አይደለም ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ላለፉት ዓመታት ተቋሙ በደረጃዎች ላይ አቅም ሲገነባ መቆየቱን ጠቁመው የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት የቴክኒካልና የሜኔጅመንት አባላትም የአገልግሎቱን ፖሊሲና ዓላማ በአግባቡ ተረድተው ለሌሎች ማስረዳትና ማብራራት ይገባቸዋል ብለዋል

የቴክኒካል ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን በአግባቡ ተረድተው ሊተረጉሟቸው ይገባል ያሉት አቶ አርአያ የአክሪዲቴሸን አገልግሎትን ለመስጠት አንድ ጊዜ ብቻ ተሰርቶ የሚያልቅ ሳይሆን በየወቅቱ እያደገ የሚሔድ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ደረጃው በትክክል ለመታየት መቻሉን መረጋገጥ ይገባል ብልዋል

በዓለም አቀፍ ደረጃው ላይ ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ጽጌ መላክ በስልጠናው ላይ እንደገለጹት ስልጠናው በዋናነት በቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት አገልግሎቱ ዓለም አቀፍ ደረጃ ግምገማ የሚደረግበት በመሆኑ ይህንን መሰረት አደርጎ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ISO/IEC 17011:2017 በቂ እውቅት እነዲኖር ለማድረግ ነው

በዓለም አቀፉ ደረጃ ላይ መሰጠት የተጀመረው ስልጠና ለቀጣዮቹ አምስት ቀናት የሚቀጥል ሲሆን ሁሉም የአገልግሎቱ የማኔጅመንት አባላትና የቴክኒክ ባለሙያዎች በስልጠናው ላይ ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ስልጠናው መመዘኛ እንደሚኖረውም በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገልጿል

ስልጠናውን የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልገሎት ዋና ደይሬክተር አቶ አርአያ ፍስሃ፣ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ጌተንት ጽጌመላክና የጥራት ሥራ አስኪያጅዋ ወ/ሮ መሰረት ተሰማ የሚሰጡት መሆኑን በፕሮግራሙ ላይ ተመልክቷል

የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ፖሊሲዎችንና ዓላማዎችን በደንብ መረዳት እንደሚገባ ተገለፀ