News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከግሎባል ኤሲአይ (Global ACI) ጋር ያለውን የባለብዙ ወገን የጋራ እውቅና ስምምነት በፊርማ አደሰየኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የአለምአቀፍ ዕውቅና ትብብር (GLOBAL ACCREDITATION COOPERATION INCORPORATED) ሙሉ አባል ሆነ::በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ግዜ ከነሐሴ 24-29/2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው ‘የኢትዮጵያ ይግዙ ‘ የንግድ ሳምንት ላይ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ለጎብኝዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡Call for Healthcare Accreditation Surveyorየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የኢስኳ ISQua ይፋዊ ሙሉ አባል በመሆን አለም አቀፍ የጤና ዘርፍ አክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት መስጠት የሚያስችለውን እውቅና አጊንቷል።የኢትዮጵያ አክሬድቴሽን አገልግሎት 17ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ።የመ/ቤቱ ሰራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱጥራትን ማስጠበቅ የሁሉም አካላት አንገብጋቢ ጉዳይ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠ

የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ማኔጅመንትና የቴክኒክ ባለሙያዎች የአገልግሎቱን ፖሊሲዎችና ዓላማዎች በአግባቡ ተረድተው አገልግሎቱን ሲሰጡ በእውቀት ላይ ተመስርተው ሊሆኑ እንደሚገባ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ገለፁ

ዋና ዳይሬክተሩ አቶ አርአያ ፍስሃ ዛሬ የካቲት 16ቀን 2014ዓ.ም በአዳማ በተጀመረው የአገልግሎቱ የማኔጅመንትና የቴክኒካል ባለሙያዎች ISO/IEC 17011:2017 በዓለም አቀፉ ደረጃ ላይ በተጀመረው ስልጠና ላይ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ለሌሎች ተቋማት ሶስተኛ ወገን በመሆን ዓለም አቀፍ ምስክርነት የሚሰጥ በመሆኑ ራሱ አስቀድሞ ዓለም አቀፉን ደረጃ በሚገባ ሊረዳ ይገባል

ብቃት በአንድ ቀን የሚገነባ አይደለም ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ላለፉት ዓመታት ተቋሙ በደረጃዎች ላይ አቅም ሲገነባ መቆየቱን ጠቁመው የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት የቴክኒካልና የሜኔጅመንት አባላትም የአገልግሎቱን ፖሊሲና ዓላማ በአግባቡ ተረድተው ለሌሎች ማስረዳትና ማብራራት ይገባቸዋል ብለዋል

የቴክኒካል ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን በአግባቡ ተረድተው ሊተረጉሟቸው ይገባል ያሉት አቶ አርአያ የአክሪዲቴሸን አገልግሎትን ለመስጠት አንድ ጊዜ ብቻ ተሰርቶ የሚያልቅ ሳይሆን በየወቅቱ እያደገ የሚሔድ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ደረጃው በትክክል ለመታየት መቻሉን መረጋገጥ ይገባል ብልዋል

በዓለም አቀፍ ደረጃው ላይ ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ጽጌ መላክ በስልጠናው ላይ እንደገለጹት ስልጠናው በዋናነት በቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት አገልግሎቱ ዓለም አቀፍ ደረጃ ግምገማ የሚደረግበት በመሆኑ ይህንን መሰረት አደርጎ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ISO/IEC 17011:2017 በቂ እውቅት እነዲኖር ለማድረግ ነው

በዓለም አቀፉ ደረጃ ላይ መሰጠት የተጀመረው ስልጠና ለቀጣዮቹ አምስት ቀናት የሚቀጥል ሲሆን ሁሉም የአገልግሎቱ የማኔጅመንት አባላትና የቴክኒክ ባለሙያዎች በስልጠናው ላይ ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ስልጠናው መመዘኛ እንደሚኖረውም በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገልጿል

ስልጠናውን የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልገሎት ዋና ደይሬክተር አቶ አርአያ ፍስሃ፣ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ጌተንት ጽጌመላክና የጥራት ሥራ አስኪያጅዋ ወ/ሮ መሰረት ተሰማ የሚሰጡት መሆኑን በፕሮግራሙ ላይ ተመልክቷል

የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት ፖሊሲዎችንና ዓላማዎችን በደንብ መረዳት እንደሚገባ ተገለፀ