News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

ሕብረተሰቡ ቅሬታ ከሚያነሳባቸው የአገልግሎት ዘርፎች አንዱ የጤና አገልግህሎቱ በመሆኑ የጤና አገልግሎቱን ማዘመንና የአክሪዲቴሽን ተጠቃሚ ማድርግ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ሊሆን ይግባል ሲሉ የኦሮሚያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለስልጣን  የሳይንስ ዘፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ገለፁ

የባለስልጣኑ የሳይንስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ልጃለም ረጋሳ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት በአዳማ የሕክምና ላቦራቶሪ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት አክሪዲቴሽን በሕክምና ዘርፍ አስተማማኝ ውጤት ለማግኘት አንዱ መንገድ ነው

መንግስት እንደሃገር ለጥራት መሰረተ ልማት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እደሆነ የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይረክተሩ የኦሮሚያ ክልልም በተለያዩ ዘርፎች ከሕብረተሰቡ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት በርካታ ትግባራት እየሰራ እንደሆነ ጠቁመው በጤና አገልግሎቱ ዘርፍም አንዱ የአገልግሎት እርካታ ያለተገኘበት በመሆኑ ትኩረት ይሰራል ብለዋል

ይህንን ዘርፍ ለማዘመንና ለማሳደግ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባ ዶክተር ልጃለም ጠቁመው የኦሮሚያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ከኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ጋር ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑንና በክልል የሚገኙ የመንግስትም ሆነ የግል የህክምና ተቋማት ስለ አክሪዲቴሸን መረጃው ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል

የስልጠናው ዋና ዓላማ ከሃገር አቀፍ ደረጃ እንዲሁም በክልሉ የሕክምና አገልግሎት ጥራትን ማሳደግ መሆኑንና ይህም ዓላማ እንዲሳካ የሁሉም ባለሙያ አስተዋጽኦ እንዲሚያስፈልግ ተናገረዋል

መረጃው ካለና በአግባቡ ግንዛቤ ከተያዘበት በቀጣይ የአክሪዲቴሸን ተጠቃሚ ለመሆን መንገዱ ይከፈታል ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ሰልጣኞች ደረጃውን በአግበቡ ተረድተው ወደ ተቋሞቻቸው ሲመለሱ ምን ሊሰሩ እንደሚገባ በማሰብ ለውጥ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል ሲሉም አሳስቸበዋል

ስልጠናው ከሰዓት በኃላ በቡድን ውይይት የቀጠለ ሲሆን በነገው እለትም በተመሰሳይ ከሰአት በፊት በደረጃው ላይ ስልጠና ከተሰጠ በኃላ ከሰአት በኃላ የቡድን ውይይት ይኖራል

የጤና ተቋማትን የአክሬዲቴሸን ተጠቃሚ ማድርግ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ሊሆን ይገባል