News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከግሎባል ኤሲአይ (Global ACI) ጋር ያለውን የባለብዙ ወገን የጋራ እውቅና ስምምነት በፊርማ አደሰየኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የአለምአቀፍ ዕውቅና ትብብር (GLOBAL ACCREDITATION COOPERATION INCORPORATED) ሙሉ አባል ሆነ::በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ግዜ ከነሐሴ 24-29/2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው ‘የኢትዮጵያ ይግዙ ‘ የንግድ ሳምንት ላይ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ለጎብኝዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡Call for Healthcare Accreditation Surveyorየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት የኢስኳ ISQua ይፋዊ ሙሉ አባል በመሆን አለም አቀፍ የጤና ዘርፍ አክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት መስጠት የሚያስችለውን እውቅና አጊንቷል።የኢትዮጵያ አክሬድቴሽን አገልግሎት 17ኛውን የሰንደቅ አላማ ቀን አከበረ።የመ/ቤቱ ሰራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱጥራትን ማስጠበቅ የሁሉም አካላት አንገብጋቢ ጉዳይ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሬዲቴሽን ጽ/ቤት ለሁለት ወላጅ አልባ ሕጻናት የትምህርት መገልገያ  ደብተር እና ቦርሳ እንዲሁም ጫማና የስፖርት ልብስ ድጋፍ አደረገ፡፡

ጽ/ቤቱ ድጋፍ ያደረገው የ2013ዓ.ም የትምህርት ዘመን መጀመርና አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድርግ ሲሆን ድጋፍ ያደረገላቸው ታዳጊዎች ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ በጽ/ቤቱ ከሰራተኞች በሚሰበሰብ ገንዘብና ከጽ/ቤቱ በሚደረግ አነስተኛ ድጋፍ የሚደገፉ ናቸው፡፡

ጽ/ቤቱ ከትምህርት ቁሳቀዩሱና ከዓልባሳቱ በተጨማሪ  ለአዲሱ ዓመት በዓልም ለያንዳንዳቸው የ800 መቶ ብር  የገንዘብ ድጋፍ ሰጥቷል፡፡

ጽ/ቤቱ ሕፃናቱ የ2ኛ ክፍል ተማሪ እያሉ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ ድጋፍ እያደረገላቸው ያሉት ተማሪዎች ሲሆኑ በዓመቱ መጀመሪያና በዓመቱ አጋማሽ ላይ እገዛዎችን ሲያደርግላቸው ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ሁለቱም ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሆነዋል፡፡

ለተማሪዎቹ እገዛ ሲደረግ ተማሪዎቹ በትምህርታቸው እንዲጠነክሩ ያበረታቱዋቸው የጽ/ቤቱ የሴቶች ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አዜብ ሰለሞን ጽ/ቤቱ በቀጣይም አቅም በፈቀደ መጠን ድጋፉን እንደሚቀጥል ጠቅሰው ተማሪዎቹ በትምህርታቸው በመጠንከር የተሻለ ደረጃ ላይ ለመድረስ ጥረት እንዲያደርጉ መክረዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ተማሪዎቹ ዩኒቨርስቲ ትምህርታቸውን እስኪያጠናቅቁ ድረስ የጀመረውን ድጋፍ እንዳማያቋርጥም ተገልጿል፡፡

ጽ/ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሁለት ወላጅ አልባ ህፃናት ድጋፍ አደረገ፡