የኢትዩጵያ ብሔራዊ አክሪዲቴሸን ጽ/ቤት ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን /March 8 / ምክንያት በማድርግ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘውን የተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድሁድ ካነሰር ድርጅት ህፃናትን ጎበኙ፡፡
የጽ/ቤቱ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ባለሙያ ወ/ሮ አዜብ ሰለሞን አስተባሪነት የጽ/ቤቱ ሠራተኞች ህጻናቱን ዛሬ የካቲት 24ቀን 2013ዓ.ም የጎበኙ ሲሆን የጉብኝቱ አላማም ህጻናቱ ያሉበትን ሁኔታ በመመልከት ሰራተኛውን በማስተባበር ድጋፍ ማድርግ የሚቻልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ነው፡፡
![](https://eas-eth.org/wp-content/uploads/2021/03/photo_2021-03-04_10-18-50-1024x768.jpg)
![](https://eas-eth.org/wp-content/uploads/2021/03/photo_2021-03-04_10-18-43-1024x768.jpg)
ሠራተኞቹ በጉብኝታቸው ለለጽዳት አገልግሎት የሚሆን ሶፍት፣ሳኒታይዘርና ፈሳሽ ሳሙና እና ከሰራተኛ የተሰበሰቡ አልባሳት ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በቀጣይም ለህጻናቱ አቅም የፈቀደውን ድጋፈ ለማድርግ እነደሚበራ ባለሙያዋ ተናገርዋል፡፡
የጽ/ቤቱ ሠራተኞች ባለፈው አመት በተመሳይ ህጻናቱን ጉብኝት ያደረጉና ድጋፍም የሰጡ ሲሆን ድርጅቱ በአሁኑ ወቅውት ህጻናቱን በተሻለ ሁኔታ ላይ እንዲገኙ ለማድርግ የሰራቸው ተግባራተ እንዳስደሰታቸው ተናገርዋል፡፡
![](https://eas-eth.org/wp-content/uploads/2021/03/photo_2021-03-04_10-18-49-1024x768.jpg)
![](https://eas-eth.org/wp-content/uploads/2021/03/photo_2021-03-04_10-18-50-1-1024x768.jpg)
![](https://eas-eth.org/wp-content/uploads/2021/03/photo_2021-03-04_10-18-01-1024x768.jpg)
![](https://eas-eth.org/wp-content/uploads/2021/03/photo_2021-03-04_10-18-50-2-1024x768.jpg)
የጽ/ቤቱ ሠራተኞች የካነሰር ድርጅት ህፃናትን ጎበኙ፡