News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ሠራተኞች በሃገር ውስጥ የያዛቸውን ዓላማዎች ለማሳካትና ዓላም አቀፍ ተቀባይነቱን አስጠብቆ ለመቀጠል የተቋሙ ባለሙያዎች ራሳቸውን ወቅቱ ከሚጠይቀው ሙያዊ ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ተናገሩ

ዋና ዳይሬክተሩ አቶ አርአያ ፍስሃ ለተቋሙ ሰራተኞች በተለወጡ የተቋሙ ሰነዶችና መመሪያዎች ላይ በተዘጋጀው ስልጠና መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት አክሬዲቴሽን  አንድ ጊዜ አውቄአለሁ ተብሎ የሚተው ተግባር ሳይሆን ሠራተኛው በየጊዜው አቅሙን ሊገነባ ይገባል

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን  አገልግሎት ዓላማዎችን ለማሳካት ዋነኛ ቁልፍ ጉዳይ የተቋሙ ባለሙያዎች ብቃትና ለሥራ ያላቸው ዝግጁነት እንደሆነ የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ ለዚህም ተቋሙ ባለፉት ዓምስት አመታት በርካታ ስልጠናዎች መስጠት መቻሉን ጠቁመዋል

ተቋሙ አሁን በ2014ዓ.ም የፌዴራል መንግስት አዲስ አደረጃጀት ተከትሎ የተቋሙ ስያሜ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን  አገልግሎት በሚል በመስተካከሉ ተቅሙ ሲሰራባቸው የነበሩ በርካታ ሰነዶችን የማስተካከል ሥራም እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል

 ሠራተኛው ለተገልጋዮቹ ብቃት ያለው አገልግሎት እንዲሰጥ ራሱ ብቃቱን በየጊዜው እያሳደገ ሊሄድ እንደሚገባ ተናገረዋል

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን  አገልግሎት በ2014ዓ.ም የያዛቸውን እቅዶች ለማሳካት የሰራተኛው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አቶ አርአያ ጠቁመው በስልጠናው የተቋሙን የዘጠኝ ወር የሥራ አፈጻጻም በመገምገም በቀሪዎቹ ሶስት ወራት ያልተፈጸሙ ተግባራት በፍጥነት በማከናወን የዓመቱን እቅድ ለማሳካት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል

ስልጠናው የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን  አገልግሎት የሚሰራበትን ፖሊሲ ማንዋል፣የሠራተኞች የተለያዩ ደንቦች፣እንዲሁም የሥራ ስነምግባርና የተቋሙ የዘጠኝ ወር አፈጻጻም ላይ በመወያየት በቀጣይ ሶስት ወር ቅድሚያ በሚሰጣቸው ሥራዎች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል

የተቋሙን ዓላማን ለማሳካት የተቋም ባለሙያዎች ራሳቸውን በሙያ ሊያሳድጉ ይገባል