News
የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በልዩ ልዩ መስኮች ዓለም አቀፍ  እውቅና አገኘ፡፡አገልግሎቱ ለግሎባል ኢንስፔክሽን ሰርቬይ ኤጀንሲ ዕውቅና ሰጠየዜና መግለጫየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት በምርት ሰርቲፊኬሽን እና በካሊብሬሽን ላቦራቶሪ አክሬዲቴሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ እውቅና አገኘአቶ ቦንሳ ባይሳ የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ላይ የአገልግሎቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የበኩላቸውን ተወጡየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት አዲሰ በተከለሰው የሕክምና ላቦራቶሪዎች ደረጃ ለመተግበር የሽግግር እቅድ አዘጋጀEthiopian Accreditation Service top management and technical staffs visited Quality Council of Indiaየኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት እንደሃገር የመጀመሪያውን የምርት ሰርተፊኬሽን እና በግሉ ዘርፍ የካሊብሬሽን ላብራቶሪ ጨምሮ አጠቃላይ ለ11 ተቋማት የላቀ ብቃት የሶስተኛ ወገን ምስክርነት የአክሬዲቴሽን ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡የኢትዮጵያ አክሪዲቴሸን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የስድስት ወር አፈጻጸም እየገመገም ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሬዲቴሽን ዳይሬክትሬት ጽ/ቤት በተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር ኢንፎርሜሽን ስርአትና እና በሌሎች ርዕሶች ላየ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡በጽ/ቤቱ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክትሬት የተዘጋጀው ይህ ስልጠና የኮቪድ ወረርሽኝን ከግንዛቤ ባስገባ መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን ሥልጠናው የሥራ ክፍሎች ዓመታዊ የግ» እቅድ ሲያዘጋጁ በተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር ኢንፎርሜሽን ስርአትና /ኢፍሚስ/ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ለመፍታት ያቀደ ነው፡፡ከዚህ በተጨማሪ የጽ/ቤቱን የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፖሊሲ መሰረት ያደረገ የጽ/ቤቱ የኢሜል አጠቃቀም ላይም ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ለመንግስት ሥራ ማንኛውም የጽ/ቤቱ ሠራተኛ የግል ኢሜል መጠቀም እንደማይችልና ይህም በፖሊሲው የተቀመጠ በመሆኑ የጽ/ቤቱን ኢሜል ብቻ ሊጠቀም እንደሚገባ አሰልጣኙ አቶ አዱኛ አብዲሳ አሳስቧል፡፡ስልጠናው ለሥራ ክፍሎች በተለያዩ ቀናት የተዘጋጀ ሲሆን መስከረም 12 ቀን 2013ዓ.ም ለጽ/ቤቱ የአክሬዲቴሸን ዳይሬክትሬት ባለሙያዎች እንዲሁም መስከረም 13ቀን 2013ዓ.ም ከተለየዩ የሥራ ክፍል ሃለፊዎች ተሰጥቷል፡፡

ጽ/ቤቱ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተሬት ለውስጥ ሰራተኞች ስልጠና እየሰጠ ነው